PIONEER IN THE PHARMACEUTICAL MANUFACTURING SINCE 1964

የኢ.መ.ፋ ሳኒታይዘር እና የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ጭንብል ምርቶች የምረቃ ስነ ስርዓት

 

የኢትዮጵያ መድሃኒት ፋብሪካ አ.ማ  ያመረታቸውን የእጅ ማፅጃ ሳኒታይዘሮችን እና የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ጭንብሎችን  ነሃሴ 9/ 2012 ዓ.ም የኢትዮጵያ  ጤና ሚኒሰቴር ዴኤታ ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ  እና የንግድ እና ኢንዱሰትሪ ሚኒስቴር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ በተገኙበት  በይፋ አስመረቀ፡፡በዝግጅቱ ላይም  ኮቪድ -19ን ለመከላከል ግንባር ቀደም ተሳታፊ ለሆኑት የህክምና ባለሙያዎች 100,000 የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ጭንብሎችን ለመስጠት ቃል  የገባ ሲሆን ቃል በገባው መሰረትም ነሃሴ 14/ 2012  የኢትዮጵያ ጤና ሚንስቴር ቢሮ በመገኘት የኢትዮጵያ ጤና ሚንስቴር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ በተገኙበት በኢ.መ.ፋ ቦርድ ሰብሳቢ በዶ/ር መሀመድ ኑሪ አመካኝነት ማስረከቡን ስንገልፅ በታላቅ ደስታ ነው፡፡

የኢትዮጵያ መድሃኒት ፋብሪካ (ኢ.መ.ፋ.) አ .ማ ማህበራዊ ግዴታውን በመወጣት

epharm

የኢትዮጵያ መድሃኒት ፋብሪካ (ኢ.መ.ፋ) ግንባር ቀደም የመድሃኒት አምራች በመሆን ላለፉት 56 አመታት የህብረተሰቡን የመድሃኒት ፍላጎት ለሟሟላት በመስራት ላይ ይገኛል ፡፡

ፋብሪካችን ማህበራዊ ግዴታውን ለመወጣት ለገጠሩ ህዝባችን የውሃ ጉድጓድ በማስቆፈር፣ ለኦቲዝም ማዕከላት ቋሚ በጀት በመመደብ ፣ለተወሰኑ የሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች በቋሚነት የምሳ ምገባ በማድረግና ሌሎች የህብረተሰቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች ለመቅረፍ ጉልህ አስተዋፆ እያደረገ ይገኛል፡፡

ኮቪድ -19 ን በመካላከል የኢ.መ.ፋ አስተዋፆ

 በአሁኑ ወቅትም በአገራችን ብሎም በ ዓለማችን ላይ እጅግ አሳሳቢ በሆነው የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ላይ ሁሌም ለ ማህበረሰቡን ችግር ፈጣን ምላሽ በመስጠት የሚታወቀው የኢትዮጵያ መድሃኒት ፋብሪካ  የበሽታውን ስርጭት ለመከላከል የሚጠቅም የእጅ ማፅጃ ሳኒታይዘር ከኢትዮጵያ ምግብና መድሃኒት ቁጥጥር ባለስልጣን መ/ቤት ፈቃድ በማግኘት የአለም ጤና ድርጅት ባስቀመጠው መመሪያ መሰረት(WHO recommended Alcohol Based hand rub solution -sanitizer ) በማምረት ለገበያ አውሏል፡፡

የምርቱ አመራረት የአለም ጤና ድርጅት ባስቀመጠው መመሪያ (Guide to Local Production: WHO-recommended Handrub Formulations) መሰረት ሲሆን በውስጡ • Ethanol 80% (v/v), • Glycerol 1.45% (v/v), • Hydrogen peroxide 0.125% D.water q.s የያዘ ሲሆን በምርት ሂደት ላይ እያለ የጥራት ማረጋገጫ ምርመራዎች የተደረጉለትና መስፈርቶቹን ያሟላ ቢሆንም በገለልተኛና በሶስተኛ አካል (National Conformity Assessment) በተደረገ የጥራት ማረጋገጫ ምርመራም  ሙሉበሙሉ መስፈርቶቹን  ያሟላ መሆኑ ተረጋግጧል፡፡

የአ.መ.ፋ የእጅ ማፅጃ ሳኒታይዘር በማምረት ያለበትን ሃገራዊ እና ማኅበራዊ ሃላፊነት እየተወጣ ከመሆኑም በተጨማሪ   ከሚመረተው ምርትም እስከ 20% የሚሆነውን ለበጎ አድራጎት ተግባር እያዋለ ይገኛል፡፡ ድጋፍ ከተደረገላቸው ውስጥም ለአብነት የሚከተሉትን መጥቀስ ይቻላል፡፡

  • ለአረጋውያን እና ለአእምሮ ህሙማን መንከባከቢያዎች (መቄዶንያ ፣ ለጌርጌሶን  ፣ለስሊዮንየ አረጋውያን ለአእምሮ ህሙማን መንከባከቢያ)
  • ለኦቲዝም ማዕከላት
  • ለአካል ጉዳተኞች ማዕከላት
  • ለፌዴራል ፖሊስና ለሌሎችም ፖሊስ ጣቢያዎች
  • ለብሄራዊ መረጃና ደህንነት ተቋም
  • ለማረምያ ቤቶች (ለቃሊቲ፤ ለቂሊንጦ እና ሌሎችም) እና
  • ለሰላም ሚኒስቴር እና ሌሎችም

በተጨማሪም ለCOVID-19 ብሄራዊ ድጋፍ አሰባሳቢ ኮሚቴ በጥሬ ገንዘብ ብር 200,000.00 (ሁለት መቶ ሺህ ብር) ዕርዳታ አድርጓል፡፡

እንደሚታወቀው በአሁኑ ወቅት ኮቪድ-19 ባስከተለው ማህበረሰባዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ምክንያት ብዙ ድርጅቶች ጫና ውስጥ ገብተዋል፡፡

የኢትዮጵያ መድሃኒት ፋብሪካ (ኢ.መ.ፋ) ይህንን ጫና በመቋቋም የኮቪድ-19 ወረርሽኝ የሚያደርሰውን የኑሮ ሁኔታ ከግምት ውስጥ በማስገባት ለሰራተኞቹ የ 1000 ብር  አና ለበዓል የሚሆን 700ብር በመስጠት ሰራተኞቹን ደጉሟል ፡፡

የኢትዮጵያ መድሃኒት ፋብሪካ (ኢ.መ.ፋ) የሚያደርገውን ድጋፍ በመቀጠል ከቶታል ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው የማህበረሰብ ክፍሎች ብዛቱ ከ90 ሺ በላይ ባለ 500ሚሊ የእጅ ማፅጃ ሳኒታይዘር በማምረት በእርዳታ መልክ ለማበርከት በዚህ ሳምንት ለማስረከብ ዝግጁነቱን ያጠናቀቀ ሲሆን ለወደፊቱም ድጋፉን አጠናክሮ ይቀጥላል፡፡

በቀጣይም የኢትዮጵያ መድሃኒት ፋብሪካ የአፍ እና አፍንጫ መሸፈኛ ጭንብሎች (Surgical Face Mask) አምርቶ በአንድ ሳምንት ጊዜ ውስጥ በተመጣጣኝ ዋጋ ለህብረተሰቡ ለማቅረብ ሙሉ ዝግጅቱን አጠናቋል ፡፡

EPHARM to Manufacture Essential Personal Protective Equipment (PPE) to Support COVID-19 Response

epharm

In keeping with its 56 -year history of answering the call for assistance in times of need, and as asocial responsible organization EPHARM was redeployed its production lines in order to manufacture essential personal protective equipment (PPE) for the community.  As it is announced before EPHARM was started to produce minimum of 30,000 L WHO recommended hand rub solution (sanitizer) per day.

Now by considering the highly need and demand for the face mask EPHARM being ready to   start production and will be available by the coming week.

የኢትዮጵያ መድሃኒት ፋብሪካ የእጅ ማፅጃ ሳኒታይዘር በማምረት ላይ ይገኛል

epharm

የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) (COVID-19) በቫይረስ ምክንያት የሚከሰት ከቀላል እስከ ከባድ የመተንፈሻ አካል ህመም   የሚያስከትል ቫይረስ ነው ፡፡በሽታው ከቀን ወደ ቀን ሊባባስ እና እንደ ሳንባ ምች (pneumonia) ከባድ የመተንፈሻ ህመም ብሎም የኩላሊት ስራ ማቆምና ሞትን ሊያስከትል የሚችል እና በአለም ላይ በከፍተኛ ፍጥነት እየተስፋፋ የሚገኝ በሽታ ነው፡፡

COVID-19 በሽታ ያለባቸዉ ሰዎች ከመጠነኛ እስከ ከባድ የመተንፈሻ ህመም ጨምሮ  ትኩሳት፣ ደረቅ ሳል  እና የትንፋሽ እጥረት  የጉሮሮ ህመም ዋነኞቹ ምልክቶቹ ሲሆኑ ከበሽታ ክብደት አንፃር መከላከል ዋነኛው አመራጭ ነው ፡፡  የመከላከያ ዘዴዎቹ ደግሞ በተደጋጋሚ እጅን በሳሙና እና በዉሃ መታጠብ ውሃ እና ሳሙና በማያገኙበት ቦታ የእጅ ማፅጃ ሳኒታይዘር  መጠቀም፣ሲያስሉ አፍና አፍንጫን በክርን  ሸፍኖ ማሳል፣ማህበራዊ ፈቀቅታን መተግበር ፣በተደጋጋሚ የሚነኩ እቃዎችንና ገፅታዎች በ አልኮል ባላቸው ማፅጃዎች ማፅዳትና ተዋስን ማስወገድ ይኖርብናል ።

በአሁኑ ሰዓት የቫይረሱ ስርጭት በከፍተኛ ፍጥነት በመስፋፋት በርካታ የዓለም ሀገራት እያስጨነቀ መሆኑ ይታወቃል ፡፡ መንግስታት ያላቸው አቅም ሁሉ ተጠቅመው  የቫይረሱን ስርጭት ለመግታት እየተንቀሳቀሱ ይገኛሉ  ፡፡    በሃገራችን ኢትዮጵያም ቫይረሱ በተወሰኑ ሰዎች ላይ መገኘቱን ተከትሎ ከፍተኛ የሆነ የጤና ማህበራዊ ኢኮኖሚያዊ ቀውስ እንዳይፈጠር መንግስትና የሚመለከታቸው ተቋማት ከፍተኛ ርብርብ እያደረጉ ይገኛሉ ፡፡ በመሆኑም ድርጅታችን  የኢትዮጵያ መድሃኒት ፋብሪካ  የበሽታውን ስርጭት ለመከላከል የሚጠቅም የእጅ ማፅጃ ሳኒታይዘር  WHO recommended hand rub solution (sanitizer ) በማምረት ካለበት ሃገራዊ እና  ማኅበራዊ ሃላፊነት  አንፃር   ከሚያገኘወ ገቢ 20% የሚሆነውን   ለአረጋውያን እና ለአእምሮ ህሙማን መንከባከቢያዎች ማረሚያ ቤቶች መቄዶንያ  የአረጋውያን ለአእምሮ ህሙማን መንከባከቢያ ፣ ለጌርጌሶን የአረጋውያን ለአእምሮ ህሙማን መንከባከቢያ ፣ለስሊዮንየ አረጋውያን ለአእምሮ ህሙማን መንከባከቢያ ለቂሊንጦ ማረምያ ቤቶች እና ለኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራያዊ ሪፐብሊክ የሰላም ሚኒስቴር  በነፃ እየሰጠ ይገኛል ፡፡

በቀጣይም የአፍ እና የአፍንጫ  መሸፈኛ ጭንብሎችን ለማምረት አስፈላጊ የሆኑ ቅድመ ዝግጅቶችን በማጠናቀቅ በቅርቡ ማምረት ይጀምራል ፡፡

epharm

የኢትዮጵያ መድኃኒት ፋብሪካ አመታዊ የሠራተኞቹን በዓል በድምቀት አከበረ!!

ጥራታቸውና ፈዋሽነታቸው የተረጋገጡ መድኃኒቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ለህብረተሰቡ በማቅረብ የሚታወቀው አንጋፋው የኢትዮጵያ መድኃኒት ፋብሪካ አመታዊ የሰራተኞቹን ቀን ጥቅምት 25/2011 ማክበሩ ተዘግቧል፡፡ በበዓሉ ቀንም የፋብሪካው የስራ ሂደት ሪፖርት የቀረበ ሲሆን የፋብሪካው ሊቀመንበር የሆኑት ዶክተር መሐመድ ኑሪ ፋብሪካው የደረሰበትን ደረጃ እና ፋብሪካው ለጥራት ከምንግዜውም በላይ ትኩረት በመስጠት ጥራታቸው የተረጋገጡ መድኃኒቶችን ማምረቱን እንደሚቀጥል እንዲሁም አዳዲስ ምርቶችን እና አዳዲስ አስተሻሸጎችን ለገበያ ማቅረቡን እንደሚቀጥል ገልፀዋል፡፡ በሰበታ የሚገኘው አዲስ እየተገነባ ያለው የፋብሪካ መስፋፊያ ሲጠናቀቅም የምርት መስመሮቹን በማሳደግ የመድኃኒት አቅርቦቱን በመጨመር ተጨማሪ የስራ እድሎችን በመፍጠርና ሀገሪቱ ላይ የሚታየውን የመድኃኒት እጥረት በመቅረፍ ረገድ ትልቅ ሚና ይጫወታልም ብለዋል፡፡ በተያያዘ ዜናም ከበዓሉ ታዳሚዎች ከተነሱ ሀሳቦች መካከል የኢትዮጵያ መድኃኒት ፋብሪካ ለህብረተሰቡ እያደረገ ያለው በጎ ተግባር የሚደነቅ መሆኑንና በዚሁ እንዲቀጥል ያላቸውን ሀሳብ በመግለፅ ሰራተኛው ድርጅቱ ያስቀመጠውን አላማ ግብ ለመድረስ ከምንግዜውም በላይ ተነሳሽ ሆኖ እንደሚሰራ ተገልፆዋል፡፡

የኢትዮጵያ መድኃኒት ፋብሪካ ከሜድቴክ ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር በመስቃንና ማረቆ ወረዳዎች ግጭት ለተጎዱት ወገኖች ድጋፍ አደረገ!!

epharm

የኢትዮጵያ መድኃኒት ፋብሪካ ከሜድቴክ ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር ሰሞኑን በመስቃን እና ማረቆ ወረዳዎች አዋሳኝ አካባቢ በተከሰተው ግጭት በሰው ህይወት እና ንብረት ላይ አደጋ በመፈጠሩ ምክንያት ከመኖሪያ ቀያቸው ለተፈናቀሉ ዜጎች መልሶ ማቋቋም በሚደረገው ጥረት እንደሁልግዜውም ሰብአዊነትን በማስቀደም አጋር በመሆኑ ግምታቸው 200000 (ሁለት መቶ ሺህ) የሆኑ የተለያዩ ህይወት አድን መድኃኒቶችን እና በጥሬ ገንዘብ 200000 (ሁለት መቶ ሺህ ብር) በድምሩ የ 400000 (አራት መቶ ሺህ) ብር እርዳታ ያደረገ ሲሆን በቀጣይነትም የተፈናቀሉት ዜጎቹን በዘላቂነት ወደ መደበኛ ኑሯቸው ተመልሰው ኑሯቸውን እስኪጀምሩ ድረስ የበኩላቸውን አስተዋፅኦ እንደሚያደርጉ የኢትዮጵያ መድኃኒት ፋብሪካ ቦርድ ሊቀመንበርና የሜድቴክ ኢትዮጵያ መስራሽ ዶ/ር መሐመድ ኑሪ ገልፀዋል፡፡

ከዚህ ቀደም በኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስትና በሶማሌ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት አዋሳኝ በነበረው ግጭት ለተፈናቀሉ ዜጎች መልሶ ማቋቋሚያ በሚደረገው ጥረት አጋር በመሆን የኢትዮጵያ መድኃኒት ፋብሪካ ለወገኖቹ በ ገንዘብ የ2000000 (ሁለት ሚሊየን) ብር ድጋፍ እና ግምቱ 4000000 (አራት ሚሊዮን) ብር የሆኑ 52 መኖርያ ቤቶችን በማስገንባት መልሶ ለማቋቋም በሚደረገው ጥረት ላይ ህዝባዊ ወገንተኝነቱን እንዳስመሰከረ ይታወሳል፡፡

 

epharm

የኢትዮጵያ መድኃኒት ፋብሪካ ከኢትዮ-ሱማሌ ክልል ከቤት ንብረታቸው ለተፈነቀሉ ዜጎች ላደረገው አስተዋፅኦ የምስክር ወረቀት ተበረከተለት!

ከዚህ ቀደም በኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስትና በሶማሌ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት አዋሳኝ በነበረው ግጭት ለተፈናቀሉ የኦሮሞ ተወላጆች መልሶ ማቋቋሚያ በሚደረገው ጥረት አጋር በመሆን የኢትዮጵያ መድኃኒት ፋብሪካ ለወገኖቹ ግምቱ 4000000 (አራት ሚሊዮን) የሆነ 52 መኖርያ ቤቶችን በማስገንባት መልሶ ለማቋቋም በሚደረገው ጥረት ወሳኝ አጋርነቱ እንዳስመሰከረ ይታወሳል፡፡ ይህንን ተከትሎም ድርጅቱ ለፈፀመው ከፍተኛ በጎ አስተዋፅኦ ከሰበታ ከተማ አስተዳደር ዋንጫና የምስክር ወረቀት ተቀብሏል፡፡

epharm

Ethiopian pharmaceutical manufacturing sh.co has participated in Dermatologic and venerology society exhibition

Ethiopian pharmaceutical manufacturing sh.co has participated in Dermatologic and venerology society which has held its 6th annual medical conference on July 26, 2018 in Addis Ababa, Ethiopia at Sheraton Addis Hotel.

A number of dermatologists and venereologist who are prescribers and potential buyers has attended this conference. EPHARM has used this opportunity to show up its various products by being sponsor, it has fully accessed an eager audience who were ready to view, use and buy its products and services.

Our company has held a very viewable and middle line booth. In this conference there were many Dermatology and Venereology Doctor Participants. And including us there were six dermatological product suppliers participated in the exhibition.

The response to our newly launched dermatology products was profoundly positive and encouraging. Concerning our old topical products the physicians reacted by stating that it is good to keep producing them because those products play greater role in keeping the skin healthy. Additionally they strongly suggest us to produce it in a sufficient amount and distribute it in a fair way. Regarding the newly launched products especially Clin-Ap (Clindamycin + Adapalin) the dermatologists feedback was very encouraging and recommended to maximize the size. They have also recommended the amendment of the strength within Sulphur with lower strength than what is now available, they prefer it to be 6%. They are also very happy about the upcoming dermatology products like Clotriplus (Clotrimazole+ hydrocortisone) and Ecort (Hydrocortisone cream).

epharm

EPHARM HAS PARTICIPATED ON ETHIOPIAN PHARMACEUTICAL ASSOCIATION (EPA) ANNUAL CONFERENCE

Ethiopian pharmaceutical manufacturing sh.co (EPHARM) has participated in EPA annual conference which was held from July 27th_28th, 2018 at African Union.
Most of the participants who were attending the meeting were health professionals, mostly pharmacists. Since EPHARM was gold sponsor, the company use this opportunity to show its new products and new presentations and creates a brand image.
EPHARM’s product banners were placed at affront view of entrance and exit to the hall. The company also held an area which was viewable in all directions. Promotional materials like (product guide lists, literature, brochures, note books Pens) which creates a brand image of EPHARM were distributed to the participants.
In the conference at least six hundred participants were attending. Great response and acceptance to our newly introduced products and presentation were seen by the audiences who also includes owner of pharmacies, wholesales and imports. They also said that new products like ClinAp, clotrimazole, hydrocortisone and Diclometh has a great market demand and good response from the prescribes as well as pharmacists.
A new product presentations like the package change and individual box were also very much appreciated.
The attendants were also amazed by the upcoming pain management drugs like pain go, pain go extra and Pramadol the packaging and the work done on branding were acknowledged.
Now a days there is a great competition in this sector so local companies should be competitor in this regard. EPAHRM is showing an ac-knowledgeable motivation in producing and distributing medications all over the country in an affordable price. They suggest to produce scares products by assessing the market and distribute it effectively.
Some of the suggestions were
• To continue with this motivation
• To address the market
• To produce the new products in mass
• To continue working on branding
• Strengthening of the sales force all over the country

epharm

የኢትዮጵያ መድኃኒት ፋብሪካ ለ ሠበታ ከተማ ነዋሪዎች የሚውል 2 ሚሊዮን ብር የሚገመት የውሃ ጉድጓድ ቁፋሮ አደረገ!

ከቄያቸው ለተፈናቀሉ የኦሮሞ ተወላጆችም ግምቱ 4 ሚሊዮን ብር የሆነ 52 መኖሪያ ቤቶችን ገንብቷል!

ሀገር በቀል የሆነውና በኢትዮጵያ ውስጥ ጥራታቸውና ፈዋሽነታቸው የተረጋገጡ መድኃኒቶችን ለህብረተሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ እያቀረበ የሚገኘው የኢትዮጵያ መድኃኒት ፋብሪካ በቅርቡ በሠበታ አካባቢ ሊገነባ ያቀደውን በአይነቱ ልዩ የሆነና በአህጉር አቀፍ የመድኃኒት ገበያ ተወዳዳሪ ያደርገዋል የተባለለትን የፋብሪካ ማስፋፊያ ፕሮጀክት ግንባታን በማስመልከት ለአከባቢው ነዋሪዎች ዋጋው ወደ 2 ሚሊዮን ብር የሚገመት የውኃ ጉድጓድ ቁፋሮ አደረገ፡፡ ይህን ተከትሎም በቅርቡ ፋብሪካውን በማስገንባት ለአከባቢው ማህበረሰብ እንደሚያበረክትም ተገልጾዋል፡፡ አከባቢው ላይ በተደጋጋሚ በሚከሰተው የውኃ እጥረት የእለት ተእለት ኑሯቸውን መግፋት ይከብዳቸው የነበሩ አንዳንድ የአከባቢው ነዋሪዎች እንደገለፁት የኢትዮጵያ መድኃኒት ፋብሪካ ያደረገው ሰናይ ተግባር የሚበረታታ እና ለህብረተሰቡ አለኝታ የሆነ ድርጅት እንደሆነ ያሳየበት ነው ብለዋል፡፡ አያይዘውም እንደገለፁት ከዚህ ቀደም በተለያዩ የበጎ አድራጎት በመሰማራት የሚታወቁት የድርጅቱ ሊቀመንበር እና የሜድቴክ ኢትዮጵያ መስራች የሆኑት ክቡር ዶ/ር መሐመድ ኑሪ ለህብረተሰባቸው እያደረጉ ለሚገኙት ተግባር እጅግ ከፍተኛ ምስጋናን እንደሚቸሩም ገልፀዋል፡፡

በተጨማሪም በቅርቡ በኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስትና በሶማሌ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት አዋሳኝ በነበረው ግጭት ለተፈናቀሉ የኦሮሞ ተወላጆች መልሶ ማቋቋሚያ በሚደረገው ጥረት አጋር በመሆን ፋብሪካው ለወገኖቹ ግምቱ 4000000 (አራት ሚሊዮን) የሆነ 52 መኖርያ ቤቶችን በማስገንባት መልሶ ለማቋቋም በሚደረገው ጥረት ወሳኝ አጋርነቱ ያስመሰከረ የክልሉ የቁርጥ ቀን አጋር ሆኗል፡፡ ለዚህ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ከኦሮሞ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የምስጋና ወረቀት ተቀብሏል፡፡
የኢትዮጵያ መድኃኒት ፋብሪካ አመራሮችም እንዲህ ላለው ተግባር ላይ የሚያደርጉትን አዎንታዊ አስተዋፅኦ አጠናክረው እንደሚቀጥሉም ገልፀዋል፡፡

1 2